Uploaded by Gossa Bekele

work ethis and good governance all house of federation 1212121

advertisement
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
Managing organizational
Ethics and good governance
The house of Federation of The
Federal Democratic Republic of
Ethiopia
March 2020
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Abdulkhalik Reshid
Senior consultant 2
Master degree in organizational
leadership
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Managing organizational Ethics and good
governance
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
EMI
Key Critical Questions for
consideration
• Do you have 5 years
of experience…or 1
year of experience 5
times?
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
ሥነምግባር ምንድን ነው?
Section 1: Ethics
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
(what is ethics ? )
ሥነምግባር ምንድን ነው?
• ሁላችንም እንደምናውቀው የሰው ህሊና እውነትን ፍለጋ
ሁልጊዜም እንዳወጣና እንዳወረደ ነው፡
• ቀድሞ ይታመንበት የነበረውን ሁሉ ከመቀበላችን በፊት
እስቲ እንመርምረው ይህ እኮ እውነት ላይሆን ይችላል
በሚል መንገድ ጥያቄ የምናነሳ ጥቂት አይደለንም፡፡
• ከምንሰማው ሁሉ እውነተኛው የትኛው ይሆን? በማለት
ከጥርጣሬ ማእበል ውስጥ ገብተን ስንጨነቅ መገኘታችን
እውቅ ነው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• ሰዎች በቀን ተቀን ህይወታችን ምርጫችን የተለያየ ነው፡፡አንዳንዱ
ከረባት አድርጎ መገኘት ሲመርጥ ሌላው ደግሞ ቀለል ያለ ልብስ
መልበስ ይመርጣል፡፡ አንዳንዶቻችን ቅመም የበዛበትን ምግብ
ስንመርጥ አንዳንዶቻችን ደግሞ ምርጫችን አይሆንም፡፡ እንዲህ
እያለ በፖለቲካ አመለካከት፣ በሀይማኖት፣ ወዘተ ዋጋ
የምንሰጣቸው ነገሮች ይለያያሉ፡፡
• የዚህ የልዩነታችን ምክንያት ምንድነው? አንዱ ዋጋ የሚሰጠውን
ሌላው ዋጋ የማይሰጠው ለምንድነው?
• አንዳንዱ ፍትህን ለማስከበር መስዋእትነት ሲከፍል ሌላው ደግሞ
ጉዳዩን በቸልተኝነት የሚያየው ለምንድነው? በመሰረቱ ለምንሰጠው
ዋጋ ከዚህ በፊት ያሳለፍነው የህይወት ተሞክሮና ልምድ ከፍተኛ
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• አንዳንድ ጊዜ ሰው ዋጋ የሚሰጠውና መልካምና ክፉ
የሚለው ነገር የግድ ያስፈልገዋል ወይ? ብለው የሚጠይቁ
አሉ፡፡አንዳንድ ጊዜ ይህ ሰው ህሊና የለውም ሲባል
እንሰማለን፡፡
• እውነት አንዳንድ ጊዜ እንደሚባለው አንዳንድ ሰዎች
ህሊና የላቸውም የሚባለው እውነት ነው?
• ስለሆነም የሰው ልጅ ምርጫ ያለው ስነምግባር ያስፈልጋል
ወይም አያስፈልግም? የሚለው ላይ ሳይሆን ምን አይነት
ስነምግባር ያስፈልገኛል? በሚለው ላይ ነው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• እንግዲያስ የአንድ ተግባር ትክክለኛነቱና መጥፎነቱ
የሚለየው በምንድነው? አንደኛውን ትክክል ሌላኛውን
መጥፎ ብለን የምንጠራው በምን ምክንያት ነው?
• በህይወታችን ዋጋ ልንሰጠው የሚገባው ነገር ምንድነው?
• በሙያችን ዋጋ ልንሰጠው የሚገባው ነገር ምንድነው?
አገራችንን ህዝባችንን በሚመለከት ዋጋ ልንሰጠው
የሚገባና ልንተገብረው የሚገባው ነገር ምንድነው?
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• የሥነምግባርን ትክክለኛ ትርጉም ለማስቀመጥ ሊያስቸግር
ይችላል፡፡ ምክንያቱም የተለያዩ ፀሐፊዎች ሥነምግባርን
በተመለከተ ልዩ ልዩ ትርጉም ስለሚሰጡት ነው፡፡
• በሌላ በኩል እኛም እያንዳንዳችን ከየእለት ተግባራችን
አኳያ የምንረዳበት እና የምንተረጉምበት መንገድ
ይለያያል፡፡
• የፀሐፊዎችን እና የሙያውን ባለቤቶች ትርጉም ለጊዜው
እናቆየውና በእኛ እና በሌሎች ግለሰቦች እይታ ያለውን
የትርጉም አሰጣጥ እንመልከት፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• የሥነምግባር ምንነትን በተመለከተ ግለሰቦች
ተጠይቀው የሰጡት መልስ ከዚህ በታች ተዘርዝሮ
ተቀምጧል፡፡
• የግለሰቦችን እይታ በጥንቃቄ ተመልከቱና ከተሰጡት
ትርጉሞች አንፃር እናንተ ከየትኛው ሃሳብ ጋር
ትስማማላችሁ?
• ሬሞንድ ባውንሃርት የተባለ የሶሾሎጂ ባለሙያ ለተለያዩ
አምስት ሰዎች “ሥነምግባር ማለት ምን ማለት ነው?”
በማለት ላቀረበላቸው ጥያቄ 5ቱም ሰዎች በየግላቸው
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ሥነምግባር ማለት ምን ማለት
ነው?”
• “ሥነምግባር ማለት ስሜቴ ትክክለኛ ነው ብሎ የሚነግረኝን ነገር
ማድረግ ማለት ነው፡፡”
• “ሥነምግባር ማለት ሀይማኖቴ የሚመራበትን እምነት እና
አመለካከት በመከተል ትክክለኛውን ነገር ማድረግ ማለት ነው፡፡”
• “ሥነምግባር ያለው ሰው ለመሆን ሕግ እንዳደርግ እና
እንዳላደርግ የሚፈቅደውን እና የሚከለክለውን በመከተል ማድረግ
ነው፡፡”
• “ሥነምግባር ማለት የትክክለኛ ምግባር መለኪያ የሆነውን እና
ሕብረተሰቡ የሚቀበለውን በመከተል ማከናወን ነው” በማለት
የመለሱ ሲሆን የመጨረሻው ሰው ደግሞ
• “ሥነምግባር ማለት ምን ማለት እንደሆነ አላውቅም” በማለት
የመለሰውን እናገኛለን፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• እያንዳንዱን ትርጉም እንመልከት ብንል ሁሉም የሥነምግባርን
የተሟላ ትርጉም የማይሰጡ እና በከፊልም የተሳሳቱ ሆነው
እናገኛቸዋለን፡፡
• የመጀመሪያው ሰው የሰጡትን ትርጉም ብንመለከት ሥነምግባር
ማለት አንድ ሰው የራሱን ስሜት በማዳመጥ ስሜቱ አድርግ
ያለውን ማድርግ ማለት እንደሆነ ገልጿል፡፡
• ይህ ከሆነ ግለሰቦች ከራሳቸው ፍላጎት እና ጥቅም ብቻ በመነሳት
ትክክለኛውን እና ሥነምግባራዊ የሆነውን ነገር ከማድረግ
ሊያፈነግጡ ይችላሉ፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• በሌላ በኩል አንዳንድ ጊዜ ስሜት ሥነምግባራዊ ከሆነው
ነገር የሚቃረንበት ጊዜ አለ፡፡ ምክንያቱም ስሜት ወደ
ውስጥ የሚመለከት፣ የራስን ፍላጎት ለማሟላት
መፈለግን እና ለዚህ መንቀሳቀስን የሚመለከት እንጂ
ሌሎች ሰዎች በጋራ ለሚመሩበት የማኅበራዊ ደህነታቸው
ለሆነው ሥርዓት የሚጨነቅ አይደለም፡፡
• ስለዚህ ይህ ትርጉም በአብዛኛው የተሳሳተ ሊሆን ይችላል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• የሁለተኛውን ሰው መልስ ስንመለከት ደግሞ በምንከተለው
ሐይማኖት መሠረት የምናምንበትን መፈፀም ብቸኛ የሥነምግባር
ትርጉም አድርጎ መውሰድን ይመለከታል፡፡
• በእርግጥ ሁሉም ሃይማኖቶች የየራሳቸው ጠንካራ የሥነምግባር
መመሪያ ያላቸው መሆኑ ይታወቃል፡፡ አባባሉን አንቀበለው ብንል
በአንድ በኩል እንደ የኃይማኖታችን የተለያየ የሥነምግባር መመሪያ
እንዲኖረን ስለሚያደርገን እንደ ዜጋ ሁሉም በጋራ የሚመራበት
አይኖርም ማለት ነው፡፡
• በሌላ በኩል ሀይማኖት የሌላቸው ሰዎች ስነምግባር የሚባል ነገር
አይመለከታቸውም እንደማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሌላ ስህተት
ውስጥ ሊጥለን የሚችል ይሆናል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• በሦስተኛ ደረጃ ከሕግ ጋር ተያይዞ የተሰጠው ትርጉምም
የተሟላ ትርጉም ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡ ምክንያቱም
የሥነምግባር ጉዳዮች በሕግ ከተቀመጡት ነገሮች በላይ
የሚሔዱ እጅግ ውስብስብ ጉዳዮችን እና በእያንዳንዷ
የህይወታችን እንቅስቃሴ የምንፈጽመውን ቅንጣት
ተግባር የሚያነሳ በመሆኑ ነው፡፡
• በሌላ በኩል አንዳንድ ጊዜ በሕግ ውስጥ የተቀመጡ ነገሮች ኢሥነምግባራዊ ሆነው በተቃራኒ
ተቀምጠው
ልናገኛቸው
እንችላለን፡፡ለምሳሌ በአሜሪካ የእርስ በእርስ ጦርነት (American Civil War) ወቅት
የነበረው የባሪያ ሕግ እና በደቡብ አፍሪካ የነበረው የነጮች አገዛዝ የነገሰበት እና በጥቁሮች
ላይ ጥሎት የነበረው ሕግ መሰል ኢ-ሰብዓዊ ሕግ ከወሰድን ሕግ ሁሉ ሥነምግባራዊ ነበር
ወይም ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• በአራተኛ ደረጃ የምናነሳው ሥነምግባር ሕብረተሰቡ የተቀበለውን
መከተል ነው የሚለውን መቀበልም ያስቸግራል፡፡ ይህንን
አካሔድ ተጠቅሞ ሥነምግባራዊ እና ኢ-ስነምግባራዊ የሆነውን
በመዘርዘር ለይቶ ለማስቀመጥ ያስቸግራል፡፡
• ምክንያቱም ሁሉንም በጥናት ለማረጋገጥ የሚያስቸግር ከመሆኑ
በተጨማሪ ሁለንተናዊ ገዥነቱ (universality) በጥያቄ ውስጥ
ይወድቃል፡፡ ሁሉም ሰው ወይም ማሕበረሰብ ያለ ልዩነት
የሚስማማበት ነገር ለማግኘት ያስቸግራል፡፡
•
በአጠቃላይ ሁሉንም በጥናት እየተደገፍን ይህ ጥሩ ነው ያኛው
ደግሞ መጥፎ ነው እያልን ለመፈተሽ አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ ስለዚህ
ስነምግባር ምን ማለት ነው? የሚለውን ለመመለስ መሠረታዊ
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• የመጀመሪያው ነገር ሥነምግባር ሰዎች ከሚኖሩበት ማሕበረሰብ
መብት እና ጥቅም አንፃር ትክክለኛ እና ትክክለኛ ያልሆኑ ነገሮችን
ለመለየት
የሚያስችል
ጠንካራ
እና
መሠረታዊ
መለኪያዎችን/መመዘኛዎችን ታሳቢ ማድረግን የሚመለከት ነው፡፡
• ለምሳሌ ፣ መስረቅ፣ መግደል፣ ማጭበርበር፣ ወዘተ … መጥፎ
ምግባሮች ናቸው ተብለው የተነቀፉ እና በአብዛኛው የሕብረተሰብ
ክፍል በመጥፎ ምግባርነት ተቀባይነት ያገኙበትን ሁኔታ ማረጋገጥ
ይቻላል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ጁዲዝ (1998) የሚባል ጸሐፊ
ሥነምግባርን ሲተረጉመው
• “እኛ ሰዎች ለሕይወታችን መመሪያ የሚሆኑትን ልዩ ልዩ
እሴቶች
እና
እነዚህን
እሴቶች
እንዴት
እንደምንጠቀምባቸው በሚያመላክቱ ገዥ መመሪያዎች
ላይ ትኩረት በማድረግ ስለተገቢነታቸው የሚያጠና
የፍልስፍና ዘርፍ ነው” በማለት ያስቀምጠዋል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ስነ-ምግባር ከተግባር ጋር የተያያዘና የተገናኘ ሆኖ ከሀሳባዊነት ባሻገር
ሰዎች በተግባር የሚሰሩት ስራ እና በሰው ባህሪ ላይ ብቻ የተመሠረተ
ነው፡፡
ስለዚህ ትክክለኛ የሆነን ነገር በማድረግ ወደ መልካም ግብ
የሚያደረስ በተለይ በህይወታችን ከውስጣችን ከሚመነጩ እሴቶችና
በሁሉም ሕብረተሰብ ዘንድ ዋጋ በሚሰጣቸውና መግባባት
የተደረሰባቸው የስነ ምግባር ዕሴቶችና መርሆዎች ድምር
ውጤት የሚመጣ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
• ሥነ-ምግባር የሚለው ቃል ethos በሚለው
የግሪክኛ ቃል ውስጥ ይገኛል ፣ እሱም ወደ “ልምዶች
(customs), ፣” “ምግባራት (conduct) ፣” ወይም
“ባህሪ (character)” ይተረጎማል ፡፡
• ሥነምግባር አንድ ግለሰብ ወይም ህብረተሰብ የሚፈለግ
ወይም ተገቢ ሆኖ ካገኛቸው እሴቶች (values) እና
ዓይነቶች ጋር ይዛመዳል ፡፡
• virtuousness of individuals and their motives.
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
ሥነምግባር
• በግላችን ምን ዓይነት ባህርይ ማሳየት እንዳለብን፣
• በአንድ ተቋም ውስጥ እንዴት ባለ ሁኔታ ስራችንን መስራት
እንዳለብን፣
• ከውስጥ ሰራተኞችና ከውጭ ደንበኞች ጋር እንዴት ባለ ሁኔታ
መገናኘት እንዳለብን፣
• በህብረተሰብ ውስጥ ስንኖር እንዴት መመላለስ እንዳለብን
ይጠቁመናል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ሲጠቃለል ሥነምግባር ማለት
• ሥነምግባር ማለት
• ጥሩ እና መጥፎ በጎ እና ክፉ ሃሳብ፣ ንግግርና
ድርጊትን የሚገልጽ ሥርዓትን የያዘ ጽንሠ ሃሳብ
ነው፡፡
• የትክክለኛና ትክክለኛ ያልሆነ ባሕርይ መለኪያ
ነው፡፡የሰው ልጅ መጥፎ የሆኑ ምኞቶች
እንዳያሸንፉትና
ፈንቅለው
እንዳይወጡ
ለመቆጣጠር የሚረዳው የሥነልቦና ልጓም ነው፡፡
• አንድ ሃሳብ ወይም ደርጊት መልካም ወይም
መጥፎ፣ ትክክል ወይም ስህተት፣ ዋጋ ያለው
ወይም ዋጋ የሌለው፣ፍትሐዊ ወይም ኢ-ፍትሐዊ
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
HOW DO YOU RATE YOURSELF WHEN IT
COMES TO ETHICS?
• all people can be categorized using the following five
statements.
1.
2.
3.
4.
I am always ethical (እኔ ሁል ጊዜ ሥነ ምግባራዊ ነኝ )
I am mostly ethical (እኔ በአብዛኛው ሥነ ምግባራዊ ነኝ)
I am somewhat ethical (እኔ በተወሰነ ደረጃ ሥነ ምግባራዊ ነኝ)
I am seldom ethical (እኔ ሥነ ምግባር የጎደለኝ ነኝ)
5. I am never ethical (እኔ መቼም ሥነምግባር የለኝም )
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የመወያያ ጥያቄ
የሰዎች እድገትም ሆነ ውድቀት በቀጥታም ሆነ
በተዘዋዋሪ ከስነ-ምግባር ጋር የተያያዘ እንደሆነ በዘርፉ
የተሰማሩ ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡
ይህንን አባባል እንዴት ታዩታላችሁ?
31
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
To be ethical in our action
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
ለጊዜያዊ ምቾት ሲባል የዘላቂ መንገድን መስዋዕት
የማድረግ ችግር
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ሥነምግባርን መማር ለምን
አስፈለገ?
• እያንዳንዱ ሰው በሙሉ ፍላጎቱ ሁልጊዜ ሥነምግባርን ጠብቆ
የሚሰራና የሚንቀሳቀስ ቢሆን ኖሮ ሥለ ሥነምግባር ጉዳይ እያነሳን
የምንነጋገርበት እና የምንጨነቅበት ሁኔታ አይኖርም ነበር፡፡
• ሥነምግባር ብዙ ጊዜ ከራሳችን የውስጥ ፍላጎት እና በተፈጥሮ ካለን
የራስ ወዳድነት / ራስን ለጥቅም ማስቀደም/ ባሕሪያችን ጋር
ይጋጫል፡፡
• ሥነምግባር ከራስ ፍላጎት ይልቅ ለሌሎች እና/ወይም ለብዙሃን
ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት እና ራሳችንን ስንጠቅም ደግሞ
የሌሎችን ጥቅም በማይጎዳ መንገድ መሆኑን ማረጋገጥ የሚጠይቅ
በመሆኑ ነው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• ይህንን አይነት ሥነምግባር የምናዳብረው ደግሞ
ሥነምግባርን በሚገባ መማር ስንችል ነው፡፡
• በሌላ አነጋገር ሥነምግባራዊ ለመሆን ወይም መልካም
ነገርን ከመጥፎ ለመለየት እና በትክክለኛ መንገድ
ለመራመድ ፣ ያለፈውን መልካም የሆነ ባሕል፣ የአኗኗር
ወግ እና ልማድ በማምጣት ለመጠቀም እና ለሚቀጥለው
ትውልድ የሚተላለፈውን ደግሞ ጠብቆ ለማቆየት
በቀደሙት ትውልዶች ሥነምግባር የየእለት ህይወታቸው
መርህ አድርገው እና አጥብቀው ይጠቀሙበት ነበር፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• አብረን በምንኖርባት ዓለም ውስጥ በጋራ ለመኖር
የሚያስችለን እና የምንመራበት ተፈጥሯዊ፣ ማኅበራዊ፣
ባሕላዊ፣ መንፈሣዊ እና አስተዳደራዊ/መንግስታዊ/ ሕግ
ሊኖረን ይገባል፡፡
• ይህንን ሕግ ደግሞ መመርመር፣ መለየት፣ መደንገግ፣ እና
መጠቀም ያስፈልጋል፡፡
• ከእነዚህ ሕጎች አንዱ የሆነው እና የማኅበራዊ ሕግ አካል
የሆነው ሥነምግባር አንዱ እና ዋናው ስለሆነ ይህንን
ማኅበራዊ ሕግ ማጥናት ደግሞ ለሕይወታችን አስፈላጊ
እና ጠቃሚ ነው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ከላይ ያየናቸው ትርጉሞች ውስጥ
ሥነ-ምግባር
• የሰውን ተግባር ባህሪና ጠባይ ትክክልና ስህተት
በማለት የሚገልጽ እንደሆነና
• ባህሪያችን/
ድርጊታችን
መቼ
ተቀባይነት
እንደሚያገኝ ወይም እንደሚያጣ የሚያመለክት
ስታንዳርድ ወይም
• የህጎች ስብስብ እንደሆነ የአንድን ግለሰብ ወይም
የሙያ አባላትን ባህሪያት የሚገዙ መርሆዎች
እንደሆነ ይጠቁማሉ
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
42
“ A man without ethics is a wild beast loosed
upon this world.” (Camus)
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
የሥነምግባር መለኪያዎች ምንድን ናቸው?
• በስፋት ስምምነት ያላቸው የሥነምግባር ባህርይ መለኪያዎች
ለምሣሌ ሃሰተኛ እና የተጭበረበረ ሰነድ አለመጠቀም፣ አለመስረቅ
የመሳሳሉ በህግ ማእቀፍ ውስጥ ተካተው ይገኛሉ፤
• ሌሎች የሥነምግባር መለኪያዎች የጥቅም ግጭት ማስወገድ፣
ሚስጢር መጠበቅን የመሳሰሉት ደግሞ በሙያ ሥነምግባር
መለኪያ ተካተው ይገኛሉ፡፡
• በርካታ የህዝብ እና የግል ተቋማት ከሠራተኞቻቸው የሚጠበቁ
የባህሪይ መለኪያዎችን ለማመልከት የሥነምግባር መመሪያ
አዘጋጅተው የሥራቸው አካል አድርገው ይጠቀማሉ፡፡
• ሥነምግባር በመንግሥት ተቋማት ወይም በህዝብ አገልግሎት
በሥነምግባር እሴቶች ላይ ተመስርቶ ባህል ሆኖ ማደግ እና
መጎልበት ይኖርበታል፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Personal and professional compass
for our actions
የመንግሥት ሃላፊዎች እና ሠራተኞች
ሊመሩባቸው የሚገቡ የሥምግባር
መርሆዎች
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
•
•
•
•
•
•
•
ቅንነት
የተሟላ/ርትኡ ስብዕና
ታማኝነት
ምስጢር መጠበቅ
ሀቀኝነት
አድልዎ አለመፈፀም
ህጋዊ በሆነ ስልጣን
መገልገል
• አርአያ መሆን
• የህዝብን ጥቅም
ማስቀደም
• ህግን ማክበር
• ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ
መስጠት
• ተጠያቂነት
• ግልጽነት
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
መልመጃ 1.1
መመሪያ
•አመቻቹ በሚሰጧችሁ መመሪያ መሰረት ቡድን መስርቱ
እና በሚከቱሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያይታችሁ ለተሳታፊዎች
በቡድኑ ተጠሪ አማካይነት አብራሩ፡፡
1. ለመሪዎች የትኞቹ የሥነምግባር መርዎች ይበልጥ
ያስፈልጋሉ ትላላችሁ?
2. የግልጽነት መርህ እና ሚስጢር መጠበቅ መርህን
እንዴት አስማምቶ ማስኬድ ይቻላል?
3. በተቋማችሁ የሥነምግባር መመሪያ አለ? በአመራሮች
እና በሠራተኞች ትኩረት ያልተሰጣቸው እና
የማይከበሩ መርሆዎች የትኞቹ ናቸው በምን ይገለጻል?
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
What is work ethics?
• A set of values that
advocate hard work and
diligence
• Emphasize the moral
benefits of work
• Said to enhance
character
• Enables workers to
differentiate the right
way of conduct from
the wrong way of
conduct.
49
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Ethics in Your Professional and Personal Life
Employees, having strong
ethics in personal and
professional life, need no
explanation, unlike those
employees for whom
work ethics is a growing
problem.
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የሥራ ሥነምግባር (Work Ethics)
• የሥራ ሥነምግባር ማለት አንድ ሠራተኛ በሥራው እንዲረካ፣
ብቃቱ እንዲጎለብት እና ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችሉ መለኪያ
መስፈርቶች ወይም ሕጎች ስብስብ ነው፡፡
• የሥራ ሥነምግባርን በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ እነዚህም
ግላዊ እና ሥራ ተኮር /ቀጥታ ከሥራ ጋር በተገናኘ/ ሲሆኑ
የተወሰኑት የሥራ ሥነምግባሮች ግላዊ ሆነው በራሳቸው
በግለሰቦች በጎ ፈቃድ የሚፈጸሙ እና ከውስጣቸው የሚመነጩ
ናቸው፤
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
መልመጃ
• ከዚህ በታች በአንድ ተቋም ውስጥ ያሉ አንዳንድ ሰራተኞች ባህርይ ቀርቧል፤
ባህርያቸው በመልካም አስተዳደር መረጋገጥ ላይ ያለውን ተጽእኖ አስረዱ፡፡
1. በተቋሙ የሚፈጸሙ ማናቸውም ነገሮች እሱን አስካልነኩት
ድረስ ምንቸገረኝ ብሎ የሚያልፍ ነው፤
2. ስራውን ውጤታማ በሆነ መንገድ ያከናውናል ነገር ግን
አብዛኛውን ጊዜ ቢሮ ውስጥ አይገኝም፤
3. ስራውን ይሰራል ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ ኢሜል እና ፌስ ቡክ
ያዝወትራል፤
4. ከመስሪያ ቤት አይቀርም ነገር ግን ለሻይ እረፍት ከወጣ ብዙ
ጊዜ አጥፍቶ ይመለሳል፤
5. ስራውም ሆነ ስነምግባሩ መልካም ነው አለባበሱ እና ጸጉር
አቆራጡ ግን ዘመናዊ ለመሆን ስለሚፈልግ የዘመኑን ዘይቤ
የሚከተል ነው፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Work ethics is an invisible employee behavior,
noticeable by its absence.
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የሥራ ሥነምግባር አውታሮች
• መልካም የሥራ ግንኙነት ጥበብ /Team
Sprit, Caring, Respect, Obedience, Serving/ Interpersonal Skills
• የሥራ ተነሳሽነት /Initiative/
• እምነት የሚጣልበት መሆን
/Dependable/
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የሥራ ሥነምግባር (Work Ethics)
መገለጫዎቹ
•
•
•
•
ለሰዎች እና ለሥራው ተገቢ ክብር መስጠት፣
ተለማጭ (Flexible) መሆን፣
ቀጠሮ አክባሪ መሆን፣
የአቋም ሰው መሆን፣ የሚሉት ሲሆኑ ከሥራው ጋር በተገናኘ
ሰራተኞች መሆን የሚጠበቅባቸውን በተመለከተ ደግሞ
ሥራው በራሱ የሚያስገድዳቸው ሁኔታዎችን የሚመለከቱ
ናቸው፡፡ መገለጫዎችም፡• በምስጢር መያዝ ያለባቸውን ነገሮች በሚስጢር
መያዝ
• ለደንበኞች ትሁት እና ቅን አገልጋይ መሆን
• አዲስ
አሰራርን እና
ተግባርን
ለመቀበል
ማዘጋጀት የሚሉት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
ራስን
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Ethical Problems are inevitable in all levels of the work
place.
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
What are the behaviors that
will almost always be viewed as
unethical?
1999
59
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Sexual intimacy with clients
1999
T.Y. LEE
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Libeling or slandering a client
62
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
ደንበኞችን መዝለፍ፣ ማንገላታት እና ተገቢ አገልግሎት አለመስጠት፣
1999
T.Y. LEE
63
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Sharing confidences without
compelling professional reasons
1999
T.Y. LEE
64
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Assaulting, causing physical injuries,
or placing clients in danger
1999
T.Y. LEE
T.Y. LEE
65
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Discriminatory practices
1999
66
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Withdrawing services precipitously
(abandoning a client)
1999
T.Y. LEE
67
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Failure to warn and protect the
victim of a violent crime
1999
T.Y. LEE
68
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Failure to exercise reasonable
precautions with a potentially
suicidal client
1999
T.Y. LEE
T.Y. LEE
69
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Promising “cures” for problems
1999
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Problem related to attitude
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የተሻለ የሥራ ሥነምግባር የሚከተሉትን ነገሮች
ማሟላት አለበት
76
ሀ. በስራ ላይ መገኘት
(attendance)
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• በሥራ ላይ ተገኝቶ መስራት ለራሱ ለሠራተኛውም ሆነ
ለቡድኑ ውጤታማነት አስፈላጊ ሲሆን በሥራ ላይ
በመገኘት ውጤታማ ሥራ መስራት ማለት፡•
•
•
•
•
ለዋናው ሥራ ከፍተኛ ትኩረት እና ቅድሚያ መስጠት፣
የሥራ ቅደም ተከተሎችን ጠንቅቆ ማወቅ፣
ከሥራ ሰዓት ዘግይቶ አለመግባት እና ቀድሞ አለመውጣት፣
የሥራ ጊዜን ለተገቢው ሥራ ማዋል፣
በችግር ከስራ ስንቀር ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ እና የመሳሰሉትን
ያጠቃልላል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ሀ. በስራ ላይ መገኘት
(attendance)
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ለ. ተገቢ ባሕሪ ማሳየት:የሚሰሩበትን መስሪያ ቤት የበለጠ ውጤታማ
ለማድረግ የሚያስችለውን ተፈላጊ ባሕሪ ማዳበር
ያስፈልጋል፡፡
• ሐቀኝነት፣
• ታማኝነት፣
• በሥራ ተፈላጊነት፣
• በሥራ ተጽእኖ ፈጣሪነት፣
• የአቋም ሰው መሆን፣
• ተነሳሽነት፣
• ሥርዓት አክባሪነት እና
• ሃላፊነትን መውሰድ
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ሐ. በቡድን ሥራ ማመን
• የቡድን ሥራ ለአንድ መስሪያ ቤት በጣም አስፈላጊ ሲሆን
መገጫዎቹም፡•
•
•
•
•
•
•
የሌሎችን መብት ማክበር፣
ተግባቢ መሆን፣
ታጋሽ እና ፅኑ መሆን፣
የአገልግሎት ሰጭነት አመለካከት መኖር፣
ከሌሎች ለመማር እና ያለንን ለሌሎች ለማካፈል ዝግጁ መሆን፣
ሚስጢር መጠበቅ እና
ለሥራ እንጂ ተገቢ ላልሆነ ጥቅም ራስን አለማስቀደም የሚሉት
ይገኙበታል፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Video
Ants crossing the river
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
What are Major Lessons learned
from the video
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Major Lessons learned
from the video
Common direction
Insistent (firm)
The desire to bring change
Determination (strength of
mind)
Commitment to common
good
Do not give up
Alignment
Team work
Coordination
Adapting situations
Problem solving skill
start and way out actions
drive
Guidance
practical wisdom
84
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
መ. ተገቢ አለባበስን መጠቀም:• አለባበሳችን ለሥራ ምቹ የሆነና የመስሪያ ቤቱ ሠራተኛ መሆናችን
የሚገልጽ እንደሁኔታው የሥራ /የደንብ/ ልብስ መልበስ ያስፈልጋል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ሠ. አመለካከት:• ለሥራ በተሰማራንበት ቦታ አዎንታዊ አመካከት፣ በራስ መተማመን
እና ለራሳችን ያለንን ግምት ከፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
87
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Importance of positive attitude
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Attitudinal problems
90
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
91
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
It is all about attitude
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ረ. ምርታማነት:• ምርታማ ለመሆን ጤናማ የሥራ ቅደም ተከተል፣ ተገቢ የሥራ
መሣሪዎች አጠቃቀም፣ ንፁህ የሥራ ቦታ እና የመሳሰሉት
መሟላት አለባቸው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ሰ. ተገቢ የሥራ ክህሎት:• ለመስሪያ ቤቶች ውጤታማ የሰዓት አጠቃቀም እና ተገቢ የሥራ
ክህሎት አስፈላጊ ግብዓቶች ሲሆኑ እነዚህ ነገሮች የግል እና የመስሪያ
ቤታችንን ሥራ በብቃት ለመወጣት ጠቃሚ ናቸው፡፡ ለዚህ መገለጫ
የሚሆኑት፡• ወደ አዲስ መስሪያ ቤት ስንገባ ለቦታው ተፈላጊ የሆኑ የሥራ
ክህሎቶችን መለየት፣
• በሥራ ላይ የሚያስቸግሩን ነገሮች ሲኖሩ መጠየቅ፣
• ለሥራው የበለጠ ጠቃሚ የሆነውን ቅድሚያ መስጠት እና
• ያከናወንነውን እና ያላከናወንነውን ነገር ለመለየት እና የቀረንን
ለማስተካከል የሚያግዙ ቅድመ ዝግጅቶችን ማድረግ፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ሸ. ተግባቦት
• ውጤታማ ግንኙነት መፍጠር እና ሌሎች ለእኛ እንዲያደርጉልን
የምንፈልገውን እኛም ለሌሎች ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ቀ. መተባበር:• መልካም የሥራ ግንኙነት መፍጠር፣ የበላይ አካል ትእዛዝን
መጠበቅ/ማክበር፣ ግጭቶችን በውይይት መፍታት እና አጠቃላይ
ችግር ፈቺ ሆኖ መገኘት አለብን፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Personal and professional compass
for our actions
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
በ. ከበሬታ
• በመስሪያ ቤቱ ውስጥ ላሉ የበላይም ሆነ የበታች ሠራተኞች በእኩል
ከበሬታ መስጠት ይጠበቅብናል፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Work ethics standard
• በስራ ላይ መገኘት
(attendance)
• ተገቢ ባሕሪ ማሳየት(
character)
• በቡድን ሥራ ማመን
(Team work)
• አመለካከት( attitude)
• ምርታማነት (
productivity)
• ተገቢ የሥራ ክህሎት:(Organizational skill)
• ተግባቦት
(communication skill)
• መተባበር
(cooperation)
• ከበሬታ
(Respect)
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Personal Reflection
Mention some of Ethical Issues
Facing your organizations
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
Ethical issues at the workplace are:
1. Conflicts of interest;
2. discrimination;
3. misuse of propriety;
4. fiddling of expense accounts;
5. misuse of organization’s assets;
6. misuse of information;
7. inaccuracies in documents and records;
8. receiving excess gifts and entertainment;
9. bribery;
10. fraud; and
11. embezzlement
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
ስኬት የተሰጠህን ሀላፊነት ያለህን አቅም ተጠቅመህ
መስራት ነው
109
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
‹‹የሰባዊነት ጥግ››
110
መጋቢት 1985 ዓ/ም‹‹ኬቨን ካርተር›› የተባለ ደቡብ አፍሪካዊ
የፎቶግራፍ ባለሙያ ሱዳን ውስጥ ተከስቶ በነበረው ርሀብ ከተባበሩት
መንግስታት የእርዳታ ልዑክ ጋር ለደግነት ወደ ደቡብ ሱዳን ያመራል ፡፡
በአንዷ መከረኛ ዕለትም ይህችን ከታች የምትመለከቷትን ምስል
በካሜራው አስቀረ፡፡ ‹‹ርሀብ አድቅቆት የገዛ ራሱን መሸከም ያቃተው ህፃን
ልጅ እና ይህን ገላ ለመግመጥ የቋመጠ ጥንብ አንሳ›› የረሀብን ክፉ ገፅታ፣
የድርቅን አሰቃቂ ሁነት፣ የምስኪኖችን እልቂት፣ ቃላት ሊገልፁ
ከሚችሉበት አቅም በላይ በሆነ መንገድ በድንቅ ካሜራው ለአለም
አስቃኘ፡፡
111
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
112
‹‹ቀጫጫ እጆች እንኳን ለመሮጥ፣ ለመቦረቅ ይቅርና የገዛ
አካሉን ለመሸከም ያዳገተው እግር፣ መቆም የከበደው ገላ እና
በርሀብ በሞቱ ሰዎች የደለበ ፈርጣማ አሞራ!!›› ይህን ፎቶ
ከወራት በኋላ በ1985 ዓ/ም ለኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ተሸጦ
ታተመ፡፡ ምስሉ በመላው አለም ታየ፡፡
ፎቶግራፈሩ፣ ክብር እና ዝናን አተረፈ፡፡ ተሸለመ፣ ተሞገሰ፡፡
ዓለም ስለፎቶግራፈሩ አወራ፡፡ ከዚህ ሽልማት በኋላ በሰጠው
ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በአንድ አስተዋይ ጋዜጠኛ የተወረወረች
ያልተጠበቀች ጥያቄ ግን የህይወቱን አቅጣጫ እስከወዲያኛው
ቀየረችው፡፡ አመሳቃቀለችው፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
113
‹‹ህፃኗ ልጅ እንዴት ሆነች….ታደግካት?!!›› አይኖቹ ፈጠጡ….ላብ
አጠመቀው………ቃላት ከአንደበቱ ጠፋ!! ………..በምናብ ወደ ደቡብ
ሱዳንዋ የርሃብ መንደር ተሰደደ፡፡ ጠያቂው ግን ድጋሚ በጩኸት ጠየቀ
‹‹ህፃንዋን ልጅ ታደግካት ??ነው ፎቶዋን ብቻ ነው ይዘኸው
የመጣህ????›› ካርተር ጋዜጣዊ መግለጫውን አቋርጦ ወጣ፡፡
ከወዳጅ ከዘመድ ሁሉ ተሰወረ፡፡ ከራሱ ጋር ተጣልቶ ለብቻው ውሳኔ
አልባ ዶሴ ከፈተ፡፡ በገዳይዋ ፊት ጥሏት የሄደው የጎስቋላ ህፃን ነፍስ
ለወራት እንቅልፍ ነሳው፡፡ ካርተር ራሱን ወነጀለ፡፡ የፎቶግራፍ ሽልማቱን
ባሸነፈ በሦስት ወሩ በልጅነቱ ሲቦርቅ ባደገባት ‹‹ፓርክሞር›› በተባለች
ለምለም ቀዬ ሀምሌ 19 1986 ዓ/ም በ33 አመቱ እራሱን ገድሎ
ተገኘ፡፡ ራሱን የሞት ፍርድ ፈረደበት ፡፡
በሞቱ ዋዜማ ላይ ሆኖ ለወዳጅ ዘመዶቹ ባስቀረው ማስታወሻ
የሚከተለውን ፀፀት አሰፈረ " ካለኝ ነገር ቀንሸ አልሰጠሁም፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
እኔን ለማኖር ስራየን ብቻ ሰራሁ፡፡ ሚጡ ከርሀብ ጋር ስትታገል
ጥንብ አንሳው በእሷ ጠግቦ ይሆናል፡፡ ሚጡዋ፣ የአሞራው እራት
ስትሆን፣ በሚጡ ርሀብ እኔ ተሸለምኩ፡፡ ይህም እኔን ሚጡ
ወዳለችበት የሞት ጎዳና እንዲሄድ ፀፀቱ አስገደደኝ፡፡ ደህና ሁኑ
ዘመዶቼ፡፡
ሰው ሲራብ፣ ሲቸገር አትዩ፡፡ ካያችሁም ከሌላችሁ ቀንሳችሁም
ቢሆን እርዱ፡፡ የህሊና ቁስል መፈወሻ የለውም፡፡
ራሳችሁን ከህሊና ቁስለት ታደጉ፡፡ "
(የሺሀሳብ አበራ) በመረጃ ምንጭነት፡new York times magazine and carter biography ን ተጠቅሜያለሁ፡፡
114
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
When Making Ethical Decisions
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
If you answered “NO”
to any of these questions,
don’t do it.
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
118
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
• ግድፈት መሥራት
• ግድፈት፣ በአሠራር ሂደት ውስጥ ተገቢውን የሥራ
ደረጃ ተከትሎ ባለመሥራት ወይም አገልግሎት
ባለመስጠት ምክንያት የሚመጣን የጥራት ችግር
ወይም ቅሬታ መብዛትን የሚያመላክት ነው፡፡
እንዲህ ዓይነቱ የሥራ ግድፈት ለዳግም ሥራ
የሚዳርግና በማንኛውም የሥራ ዓይነት ላይ
የሚያስከትለው ተፅእኖ ከፍተኛ የሆነ ነው፡፡
ስለሆነም፣ በሥራ ሂደት የተቀመጡ አሠራሮችን እና
ደረጀዎችን በትክክል መከተል ያስፈልጋል፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
EMI
121
EMI
122
EMI
123
EMI
124
EMI
125
EMI
126
EMI
127
EMI
128
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
መልካም አስተዳደር
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
Solving problems differently
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
የመልካም አስተዳደር ጽንሰ-ሃሳብ
• መልካም አስተዳደር ከ1990ዎቹ ቀደም ሲል የነበሩ የህዝብ አመራር
ዘይቤዎች (Traditional bureaucratic public management) በዋናነት
የመንግስት አፈጻጸም ውጤታማና ቀልጣፋ ከማድረግና
• ሙስናና ቢሮክራሲያዊ አሰራር ችግሮችን ከመፍታት አንጻር ክፍተት
የሚታይባቸው በመሆኑ ይህን ክፍተት ለመድፈን
• የመንግስት ተቋማትና የህዝብ አገልግሎቶቹ ቅልጥፍና
እንዲጨምር፣
• የመንግስት አመራር የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን
• የመልካም አስተዳደር ጽንሰ ሀሳብ እንደ አንድ የፐብሊክ አመራር
አማራጭ ብቅ ማለቱንና
• በሁሉም የአለም አገራት ዘንድ ልማትን ለማረጋገጥ ትኩረት
ያገኘ የአመራር ሥርዓት እንደሆነ ብዙዎች ይገልጻሉ፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
መልካም አስተዳደር ምንድነው
• ስለ መልካም አስተዳደር ምንነት አንድና ወጥ
ትርጉም ማግኘት ያስቸግራል፡፡
• መልካም የሚለው ቃል የተወሰነ መለኪያ የሌለው
በመሆኑ መልካም አስተዳደርን ከመተርጎም
መገለጫ ባህሪያቱን ማሳየት የተሸለ እንደሆነ
ብዙዎች ይስማማሉ፡፡
• በዚህ መሰረት የተለያዩ ጸሐፊዎችና ዓለም አቀፍ
ተቋማት ለመልካም አስተዳዳር ተመሳሳይና
ተቀራራቢ መገለጫዎችና ትርጉም ሰጥተዋል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
መልካም አስተዳደር ምንድነው
የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም
UNDP (1997 እ.ኤ.አ) መልካም አስተዳደር
• የአንድን አገር ጉዳዮች አሳታፊ፣ ግልጽ፣ ተጠያቂነት፣
ውጤታማ እና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለማስተዳደር
ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ስልጣንን
መጠቀም እንደሆነ ይገልጻል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
መልካም አስተዳደር ምንድነው
የአለም ባንክ (2008) መልካም አስተዳደር
• ግልፅነትና ተጠያቂነትን፣ ቅልጥፍናንና ውጤታማነትን፤
የህግ የበላይነትንና መንግስታት ከህዝባቸው ጋር
የሚኖራቸው መልካም የፖለቲካ ግንኙነትን እንደ ዋነኛ
የመልካም አስተዳደር መገለጫ አድርጎ ይወስዳል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
መልካም አስተዳደር ምንድነው
USAID (2005) ፣መልካም አስተዳደር
• መንግስት ወጭ ቆጣቢ፣ ውጤታማና ተጠያቂነት
ያለው የህዝብ አስተዳደር ለማጎልበት ያለዉ አቅም
የሚመለከት ሲሆን መገለጫዉም ግልፀኝነት፣
ብዝሃነት፣ የዜጎች በውሳኔ አሰጣጥ ላይ መሳተፍ፣
ዉክልናና ተጠያቂነት እንደሆኑ ያስረዳል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
በአጠቃላይ ከላይ ከቀረቡት ሃሳቦች
መልካም አስተዳደደር
• ለዘላቀ ልማት የአገር
ሀብት በግልጽነትና
በተጠያቂነት
የሚመራበት፣
• የህዝብ ጥቅምና
ፍላጎት የሚገለጽበት፣
• የህዝቦች ፖለቲካዊ
ማህበራዊ እና
ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎና
ተጠቃሚነት
የተረጋገጠበት፣
• ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ
የሚሰጥበት፣
• የህግ የበላነትና
ተጠያቂነት ያለበት፣
• አሳታፊና ሙስናን
መቆጣጠር የሚያስችል
አስተዳደራዊ ሥርዓት
ማለት እንደሆነ
መገንዘብ ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
የመልካም አስተዳደር መሠረታዊ
መርሆዎችና አስፈላጊነት
EMI
ቀጣይ የሚመጣው ምልክት ምን ይመስላቹኀል
EMI
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
የመልካም አስተዳደር መሰረታዊ
መርሆዎች
• የተለያዩ የልማትና የፋይናንስ ዓለም አቀፍ ተቋማት
ከራሳቸው እይታ አንጻር የመልካም አስተዳደር
መገለጫ ባህሪያትን ወይም መርሆዎችን ይገለጻሉ፡፡
• በአገራችን መልካም አስተዳደርን በተሟላ ሁኔታ
ለማስፈን ሁሉም መርሆዎች እኩል ትኩረት
ተሰጥቷቸው ተሳስረውና ተመጋግበው ተግባራዊ
በመደረግ ላይ ናቸው፡፡
• ከዚህ ባሻገር መርሆዎቹ ከዴሞክራሲያዊ ስርዓት
ግንባታና ከልማት ጋር ተያይዘው የሚፈጸሙ ናቸው፡፡
በመሆኑም
በአገራችን በመተግበር ላይ ያሉት
መርሆዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
የመልካም አስተዳደር መሰረታዊ
መርሆዎች
• አሳታፊነት
(Participatory)
• የህግ የበላይነት
(the Rule of Law)
• ግልጽነት
(Transparency)
• ተጠያቂነት
(Accountability)
• ምላሽ ሰጪነት
(Responsiveness)
• ስምምነት ተኮር
(Consensus Oriented)
• ፍትሃዊነትና
አካታችነት (Equity and
Inclusiveness)
• ውጤታማነት እና
ቅልጥፍና (Effectiveness
and Efficiency)
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
1. አሳታፊነት (Participatory)
• የሲቪል ማህበረሰቡ፣ የተለያዩ ቡድኖች እና መላው ህብረተሰብ በአገር
ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ የሚችሉበት
ልምድና አሰራር እንዲኖር ይጠይቃል::
• ህዝብ በመንግሥት ፖሊሲዎች፣ የልማትና ማህበራዊ ፕሮግራሞች፣
በአካባቢያቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ተሳትፎ ሊኖራቸው ይገባል፡፡
• የህዝብ ተሳትፎ የሌለበት የልማት ሥራ ውጤታማ አይሆንም፡፡ ተሳትፎው
በቀጥታ ወይም ፍላጎታቸውን በሚወክሉ አካላት ሊሆን ይችላል፡፡
• ህዝብ መንግሥታዊ አገልግሎት በሚሰጥባቸው ተቋማት አሰራር ላይ አስተያየት
የሚሰጥበት፣ ዕቅድና አፈፃፀምን የሚገመግምበት እና በሁሉም የአመራር ሂደቶች
በባለቤትነት ተሳትፎ የሚያደርግበት አሰራር የመልካም አስተዳደር መገለጫ
ባህሪይ ነው፡፡
• ይህ የመልክም አስተዳድር ገጽታ ለመንግሥት የልማትና ማህበራዊ እቅዶች
ተግባራዊነት እና የአፈፃፀም ጥራት ለማሻሻል ወሳኝ ሚና ይጫወታል::
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
2.የህግ የበላይነት (Follows the Rule of
Law)
• ዜጎች ያለምንም አድሎና ልዩነት በህግ ፊት እኩል የሚዳኙበት፣ መብቶችና
ጥቅሞቻቸው በእኩል የሚጠበቅበት ሥርዓት መሠረት የሆነ መርህ ነው፡፡
• ሁሉም ዜጎች በህግ ፊት እኩል የሚዳኙበት የህግ የበላይነት መከበር
የሚያረጋገጥበት የአስተዳደር ሥርዓት ነው፡፡
• የሕግ ማዕቀፎች ፍትሃዊ መሆን ብቻ ሣይሆን የሰብአዊ መብት ህጎችና ሌሎች
ህጎች ያለአድሎና በተገቢው መንገድ መከበርን ህጋዊ ግዴታቸውን የማይወጡ
አካላት የሚጠየቁበት ህጋዊ አሰራር እውን መሆንን የሚጠይቅ ሥርዓት ነው፤
በመሆኑም የህግ የበላይነት የመልካም አስተዳደር መርህና ዋነኛ መገለጫ ባህሪው
ነው፡፡
• ሁሉም ዜጋ በህግ ፊት እኩል መሰተናገድን ብቻ የሚመለከት ሳይሆን የመንግሥት
አገልግሎት በቅድሚያ ተለይተው በሚታወቁ የህግ ማእቀፎች በህግ አግባብ
መሰጠትንም የሚመለክት ነው፡፡
• በመሆኑም የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ በቅድሚያ ተለይተው በሚታወቁ
ህግና ደንብ ወጥና ፍህታዊ በሆነ መንገድ ለዜጎች ሁሉ መሰጠት ይኖርባቸዋል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
3.ግልጽነት (Transparency)
• ግልፅነት የመልካም አስተዳደር መሠረታዊ መገለጫ መርህ ነው፡፡ ግልጽነት
ዜጎች የመንግሥት አሰራርና ውሳኔዎች ለህብረተሰቡ ግልጽ የሚሆንበት፣ ህዝብም
ስለመንግሥት አሰራር የሚያውቅበት እና ቁጥጥር የሚያደርግበት አሰራርን
የሚመለከት መርህ ነው፡፡
• በመንግስት አሰራር ውስጥ ግልጽነት የመንግሥት አገልግሎት የሚመራበትን ህግና
ደንብ፣ እንዲሁም መንግሥት ለልማትና ለህዝብ አገልግሎት የሚመድበውን
በጀትና የበጀት አጠቃቀም የሚመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎች ለህዝብ ግልጽ
ማድረግን ያካትታል፡፡
• መልካም አስተዳደር ደግሞ ዜጎች የመንግሥት አሰራርና ውሳኔዎች ግልጽ
የሚሆንበትና ህዝብም ስለመንግሥት አሰራር የማወቅና መረጃ የማግኘት መብት
የሚከበርበት አሰራር መኖርን ይጠይቃል፡፡
• ሕዝቡ በመንግስት አሰራርና ውሣኔዎች ላይ በብቃት መሳተፍ እና መቆጣጠር
እንዲችል መንግሥት ለልማትና ለህዝብ አገልግሎት ስለሚመደቡ በጀትና
አጠቃቀም ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ ማግኘት ይኖርበታል፡፡
• በግልጽነት የአሰራር ስርአት ህብረተሰቡ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ማግኘት ከቻለ
አሰራሮች ሁሉ ግልጽ ስለሚሆኑ የአስተዳደር በደል፣ ብልሹ አሰራር፣ ሙስናና
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
4. ተጠያቂነት (Accountability)
• ተጠያቂነት በተሰጠ ህዝባዊና መንግስታዊ ሃላፊነት ላከናወኑት ተግባር፣ ለወሰኑት
ውሳኔና ለተገኘ ውጤት በጋራና በግል ሃላፊነት መወሰድና ተጠያቂ መሆንን
የሚመለከት ነው፡፡
• የተጠያቂነት መርህ መንግሥት፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት እና ሠራተኞች
የተሰጣቸውን ተግባርና ሃላፊነት በአግባቡ ባልተወጡ ጊዜ ተጠያቂ የሚሆኑበት፣
ላከናወኑት ተግባር፣ለሚወስዷቸው እርምጃዎች እና ውሳኔዎች ሃላፈነት
የሚወስዱበት እና ተጠያቂ የሚሆኑበት ሥርዓት ነው፡፡
• ተጠያቂነቱ ከፖለቲካ፣ ከሕግ፣ ከገንዘብ፣ ከአስተዳደር ወዘተ ሊሆን ይችላል፡፡
በተጠያቂነት ሥርዓት መንግሥትና የመንግሥት አካላት ብቻ ሳይሆኑ የሲቪክ
ማህበራትና የግሉ ሴክተርም በሚያከናውኑት ተግባራትና በሚወስዱት
እርምጃዎችና በሚያገኙት ውጤት ለህዝብ ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
5. ምላሽ ሰጪነት (Responsiveness)
• ምላሽ ሰጪነት
መስጠትን፣
ተገቢ፣
ወቅታዊና
ፈጣን
አገልግሎት
• በመንግሥት ተቋማት አሰራርና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ዜጎች
የሚያነሷቸው ጥያቄዎች፣ ነቀፌታዎችና አስተያየቶችን
መቀበልና ተገቢውን መልስ መስጠት የሚመለከት ነው፡፡
• ፈጣን አገልግሎት የሚሰጡበት፣ በአሰራራቸው ላይ ተገልጋዩች
ቅሬታና አሰተያየት የሚሰጡበት ሥርዓት በመዘርጋት ፈጣን
ምላሽ የሚሰጥበት ሥርዓት ነው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
6. ስምምነት ተኮር (Consensus
Oriented)
• መልካም አስተዳደር የተለያዩ ፍላጎቶችና አመለካከቶች የሚሰተናገዱበት፣ የተለያዩ
ፍላጎቶችን በማጣጣም አገራዊ በሆኑ ጉዳዮች በዜጎች መካከል የጋራ ስምምነት
መፍጠር የሚያስችል አሰራር ላይ የሚመሰረት ሥርዓት ነው፡፡
• በህብረተሰቡ ውስጥ የሚከናወኑ ማንኛውም ተግባራት በጋራ ስምምነትና
መግባባት ያገኘ ሊሆን ይገባል፡፡ ይህም ለአንድ ዓላማና ግብ በጋራ መንቀሳቀስና
ውጤት ለማምጣት ያስችላል፡፡
• መልካም አስተዳደር የተለያዩ ፍላጎቶችና አመለካከቶች በሠላማዊና ዲሞክራሲያዊ
መንገድ በማስተናገድ የጋራና መሰረታዊ በሆኑ በልማት፣ በሀገር ደህንነትና መሰል
ጉዳዮች በህዝቦች መካከል የጋራ መግባባት መፍጠር መርህን መሰረት ያደረገ
ሥርዓት ነው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
7.ፍትሃዊነትና አካታችነት (Equity and
Inclusiveness)
• ዜጎችን በጾታ፣ በሃይማኖት፣ በዘርና በጎሳ፣ በፖለቲካ አመለካከት እና ባላቸው
ማህበራዊ ቦታ ልዩነት ሳይደረግ የሀገርን ሀብትና ንብረት በእኩል ተጠቃሚ
የማድረግ መርህ ነው፡፡
• ዜጎች በመንግሥታዊ አገልግሎት ያለ አድልዎና ልዩነት እንዲገለገሉ፣
እንዲስተናገዱና ጥያቄና ቅሬታቸው በህግ አግባብ ምላሽ የሚያገኙበት አሰራር
ነው፡፡
• የፍትሃዊነት መጓድል በዜጎች መካከል አድሎና ልዩነት ስለሚፈጥር ለሙስናና
ብልሹ አሰራር ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ይህም በዜጐች ዘንድ ቅሬታን በመፍጠር፣
የመንግሥትን አመኔታ ያሳጣል፣ ህዝባዊ አመጽን ያስከትላል፤ ሠላምን ያሳጣል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
8.ውጤታማነት እና ቅልጥፍና
(Effectiveness and Efficiency)
• ቅልጥፍናና ውጤታማነት የአገር ሀብትና ገንዘብን ከብክነት በጸዳ መልኩ
በመጠቀም በአጭር ጊዜ የሀገርና የህዝብ ጥቅምና ፍላጎት ለማሟለት
የሚበጅ ተግባራትን በብቃት መፈጸምን እና የህዝብን ተጠቃሚነት
ማረጋገጥን የሚመለከት መርህ ነው፡፡
• መንግሥት ለዜጎች ህግና ደንቦችን ከማውጣት ባሻገር ጥራት ያለው ፈጣን
ማህበራዊ አገልጎቶችን የማቅረብ ሃላፊነት አለበት፡፡ ህዝብም ፈጣን፣ ቀልጣፋና
ጥራት ያለው አገልግሎት የማግኘት መብት አለው፡፡ ይህን የህዝብ መብት
ለማስጠበቅ ፈጣን፣ ቀልጠፋና ውጤታማ አገልግሎት ለህዝብ መስጠት መቻል
ያስፈልጋል፡፡ ለዚህም መልካም አስተዳዳርን ማጎልበት ግድ ይላል፡፡
• ውስን የሆነዉን የሰዉና የፋይናንስ ሀብት በተገቢ መልኩ ጥቅም ላይ በማዋል፣
ከሀብት ብክነት እና ከሙስና የጸዳ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ውጤታማ የህዝብ
አገልግሎት መስጠት መለያ ባህሪው ነዉ፡፡
• የአገር ሀብት በአግባቡ በመጠቀም የህብረተሰቡን ፍላጎት ሟሟላት
የሚያስችል ውጤታማ ተቋማዊ አሰራር መኖር ማለት ነው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ኬዝ አንድ
• አቶ ሠለሞን የአንድ አውራጃ አስተዳደሪ ናቸው፡፡ አቶ ሰለሞን የአስተዳደሩን
የማናጅመንት አባላት ሰብሰበው የአውራጃውን የልማት እቅድ ያቅዳሉ፤ ከእቅዳቸው
መካከል በአውራጃው ለሚገኘው የለምለም ቀበሌ አርሶ አደሮች ጤና ጣቢያ
መስራት አንዱ ነው፡፡ እቅዳቸውን ለማስፈጸም ወደ ለምለም ቀበሌው በመሄድ
የቀበሌው ሊቀመንበር ህዝቡን እንዲሰበስብላቸው ያድጋሉ፡፡
• ለህዝቡም አዚህ የተገኘውት ለዚህ ህዝብ ያስፈልጋል ያልኩትን የጤና ጣቢያ ግንባታ
ለማስጀመር ነው በማለት ከገለጹ በኃላ ለግንባታው እያንዳንዱ አባወራ አምስት
አምስት መቶ ብር እንዲዋጣ፣ ለግንባታው ምቹ የሆነ ቦታ ተመርጡ ይዞታው የሆነ
ነዋሪ እንዲሰጥ ይህንን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያስፈጽሙ የአምስት ሰዎችን
ሰም ጠርተው እንድታስፈጽሙ ብለው ወደ መጡበት ይመለሳሉ፡፡
• በወሩ ሥራው ምን እንደደረሰ ለመመልከት ሲመጡ የተመረጡት ሰዎች ህዝቡ
እምቢተኛ መሆኑንና እንደውም አመጽና ተቃውሞ ለማስነሳት እየተዘጋጀ እንደሆነ
ይገልጹላቸዋል፡፡
1. ይህን ኬዝ ከመልካም አስተዳደር መርሆዎች አንጻር መዝኑ?
2. የለምለም ነዋሪዎች ጤና ጣቢያ ግንባታ የልማት ሥራን ያልተቀበሉት
ለምንድ ነው?
3. የተጣሱ የመልካም አስተዳደር መርሆዎች የትኞቹ ናቸው?
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
የመልካም አስተዳደር መስፈን ያለው
ጠቀሜታ
• የመልካም አስተዳደር መስፈን
• የስልጣን ምንጭና ባለቤት የሆነው ህዝብ በተወካዮቹ ላይ እምነት
እንዲያሳድር ማድረጉ
• በመንግስት በሚተላለፉ ውሳኔዎች ላይ እምነት እንዲጥልና
• ለተግባራዊነቱም እንዲረባረብ በማድረግ ውጤታማ የማህበራዊ ፣
የኢኮኖሚያዊ እና የፖለቲካዊ ስኬቶችን ማረጋገጥ ያስችላል፤
• ህዝቡ የኔነት መንፈስ እንዲያድርበትና በመንግስት ላይ ያለው አመኔታ
እንዲጨምር ያድርጋል፡፡
• የሚወስኑት ውሳኔዎች በህዝቡ ዘንድ የሚኖራቸው ተቀባይነት እየጨመረ
ስለሚሄድ ውሳኔ ሰጪው የመንግስት አካል በራስ የመተማመን መንፈሱ
እያደገ ይሄዳል ማለት ነው፡፡
• የመንግስት
ተቋማት
አመራሮች
በመረጣቸው
ህዝብ
ዘንድ
ተቀባይነታቸው እንዲያደግ ያደርጋል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
መልካም አስተዳደርን በማስፈን ረገድ የፐብሊክ
ሰርቪሱ ሚና
• ፐብሊክ ሰርቪሱ መልካም አስተዳደር የማረጋገጥ ስራዎች አፈፃፀም
የሚመዘንበትን ስርዓት በመዘርጋት ተግባራዊነቱን የማረጋገጥ ሚና
አለው፡፡
• የፐብሊክ ሰርቪስ ተቋማት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን
በመለየት እና መፍትሄዎችን በማስቀመጥ ትንተና ላይ የተመሠረተና
ሁሉንም ሰራተኛ ያሳተፈ የየራሳቸውን የመልካም አስተዳደር ዕቅድ
በማዘጋጀት ተግባራዊ ማድረግና በባለቤትነት መምራት
ይጠበቅባቸዋል፡፡
• ከዚህ በተጨማሪ የመልካም አስተዳደር ዕቅድ አፈፃፀም ላይ
ክትትልና ድጋፍ በማድረግ የእቅድ አፈጻጸም ውጤታማ እንዲሆን
የመደገፍ ስራ ማከናወን ይገባቸዋል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ
መንግሥት በየጊዜው የሚያወጣቸውን ፖሊሲዎች፣ ስትራተጂዎች፣
ፕሮግራሞችና ዕቅዶች መረዳትና በባለቤትነት መፈፀም ይገባዋል፡፡
• በመልካም አስተዳደር ዕቅድ ዝግጅትና አፈጻጸም ወቅትና ህዝቡ
የሚያነሳቸው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ሂደት
ውስጥ በንቃት መሳተፍ ይኖርባቸዋል፡፡
• የመስሪያ ቤታቸውን የውስጥ የመልካም አስተዳደር ችግሮች
በመፍታት ሂደት ውስጥም ተመሳሳይ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ
ይጠበቅባቸዋል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
የህዝብ ም/ቤቶች ሚና
• በየደረጃው የሚገኙ የህዝብ ም/ቤቶች የመልካም አስተዳደር ዕቅድ
ዝግጅትና ዕቅድ አፈጻጸምን በቋሚ ኮሚቴዎቻቸው አማካይነት
ራሱን አስችሎ የመከታተል፣ የመቆጣጠር፤ የመደገፍ፣ በተቋማት
በአካል በመገኘት የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ሱፐርቫይዝ
ማድረግ ሚናቸውን ይወጣሉ፡፡
• የመልካም አስተዳደር ስራን ከሚያስተባብሩ የመንግስት ተቋማት
ጋር በመሆን በክልሎች፣ በከተሞችና በታችኛው የአስተዳደር እርከን
ያለውን የመልካም አስተዳደር ዕቅድ አፈጻጸም ሱፐርቫይዝ
ከማድረግ አኳያም የህዝብ ተወካዮች ሚና የጎላ ነው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
የመልካም አስተዳደር ዕቅድ
ዝግጅት እና ትግበራ
• በየተቋማቱ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን
በዘላቂነትና ትርጉም ባለው መልኩ ለመፍታት የሚከናወኑ
• የነባራዊ ሁኔታን የመዳሰስ፣
• የመልካም አስተዳደር ችግሮችንና፣ የትኩረት ነጥቦችን የመለየት፣
• የተለዩ ችግሮችን የመመዘንና ቅደም ተከተል የማስያዝ፣
• ስትራቴጂያዊ ግቦችንና ግብ ተኮር ተግባራትን የመቅረጽ፤
• ዝርዝር የትግበራ መርሃ ግብርን የማዘጋጀትና የሌሎች ተያያዥ
የእቅድ ተግባራት እንደ አገር ከምንከተለው ውጤት ተኮር
የአፈፃፀም አመራር ስርዓት
መርሆዎች ጋር መጣጣምና
መደጋገፍ ይገባቸዋል፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
የመልካም አስተዳደር ችግሮች
ምንነት
• የመልካም አስተዳደር ችግሮች ከመልካም አስተዳደር መርሆዎች
አለመተግበር የሚመነጩና በመርሆዎቹ አተገባበር ጉድለት
ምክንያት የሚፈጠሩ ናቸው፡፡
• የመልካም አስተዳደር ችግሮች የመንግስት ተቋማትን የእቅድ
ክንውን ክፍተቶች ከመሰረታዊ የመልካም አስተዳደር
መርሆዎች አንጻር በመገምገም የሚለዩ ይሆናሉ፡፡
• ተቋማት ለተገልጋዮቻቸው ከሚሰጡት አገልግሎት ጋር ተያይዞ
ሊከሰቱ የሚችሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የውስጥ እና የውጭ
ተብለው ይለያሉ፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• የውስጥ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚባሉት
የመንግስት
ተቋማት
ለውስጥ
ተገልጋዮቻቸው
ከሚሰጧቸው አገልገሎቶች ጋር ተያይዞ የተቋሙ ሰራተኛ
የሚያነሳቸው ችግሮች ናቸው፡፡
• ችግሮቹም በዋናነት ከሰው ሃብት ስራ አመራር ጉዳዮች
(ቅጥር፣ ደረጃ እድገት፣ ዝውውር፣ ስንብት፣ ወዘተ)፣
ከግብአት አቅርቦት፣ ከተሳትፎ፤ ከአፈጻጸም ምዘና፣
ከስልጠናና የትምህርት እድል እና ከመሳሰሉት
አገልግሎቶች ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ ናቸው፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚባሉት የመንግስት
ተቋማት አገልግሎት ፈልገው ወደ ተቋማቱ ለሚመጡ የውጭ
ተገልጋዮች ከሚሰጧቸው አገልገሎቶች ጋር ተያይዘው የሚፈጠሩና
ተገልጋዮቹ የሚያነሷቸው ችግሮች ናቸው፡፡
• ችግሮቹም በዋናነት ዜጎችን በአግባቡ ካለማሳተፍ፣ ፈጣን፤
ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ካለመስጠት፤ የግልጽነትና
ተጠያቂነት አሰራርን ከማጓደል፣ ፍትሃዊ እና አካታች አገልግሎት
ካለመስጠት፣ ከህጎች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች መጣስ እና
ከመሳሰሉት ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡
• በየደረጃው ከልማትና ከመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ
ዜጎች የሚያነሱዋቸው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመለየት
ቀጥሎ የቀረቡ ዋና ዋና ስልቶች እንደአስፈላጊነታቸው በጣምራ
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
• የመንግስት ተቋማት ከላይ የተዘረዘሩትንና ሌሎች አማራጭ
መንገዶችን (የመረጃ ምንጮችን) በመጠቀም የውስጥ እና የውጭ
የመልካም አስተዳደር ችግሮቻቸውን በአግባቡ መለየት አለባቸው፡፡
• የተለዩትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች በቅደም ተከተል
በማደራጀት ሊፈቱ የሚችሉበትን አግባብ (ስልት) ጭምር በመለየት
ዝርዝር የመፍቻ ዕቅድ መንደፍ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም ይህንን ስራ
በውጤታማነት ለመተግበር የሚከተሉትን ሂደቶች መከተል ጠቃሚ
ይሆናል፡፡
• በተያዘው የበጀት ዓመት የሚፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን
ለመፍታት የሚከናወኑ ተግባራትን በአጭር፣ በመካከለኛ እና
በረጅም ጊዜ በመሸንሸን ዝርዝር የድርጊት መርሀ ግብር ማዘጋጀት፡፡
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
ዝርዝር የመፍቻ ዕቅድ
• የተለዩ ችግሮችን
እንደወረዱ ማስቀመጥ፣
• የችግሮችን መንስኤ
መለየት፣
• ችግሮችን እንደ የክብደታቸው
(እርካታ የመፍጠር ተጽእኖ
ገዥነት፣ አንገብጋቢነት፣
የሚያስከትለው አደጋ፣ የተጣሱ
መርሆዎች ብዛት፣ ወዘተ)
በቅደም ተከተል ማስቀመጥ፣
• ተመሳሳይ መንስኤ
ያላቸውን ችግሮችን
በየፈርጃቸው ማደራጀት፣
• ችግሮችን ከመልካም
አስተዳደር መርሆዎች
አንጻር ለይቶ መፈረጅ
• ተመሳሳይ መንስኤ
ያላቸው ችግሮችን
ለመፍታት የሚያስችሉ
ስትራቴጂያዊ ግቦችን
መቅረጽ፣
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
5 Whys Example in the Lean
Office
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
Tree diagram for identifying
cause and effect
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
Case for illustration
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
169
የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት
Ethiopian Management Institute
EMI
ኢ.ሥ.ኢ
Develop personal goals
list three (or more) personal goals for improving your work ethics
and good governance approach
Download